Gadaatu Fala
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Gadaatu Fala, Health/Beauty, Shaggar, Addis Ababa.
የምንጊዜም ምርጫችን ሰላም ነው!
12/12/2023
የሀገር መከላከያ ልዩ ኦፕሬሽን በኦሮሚያ
የሀገር መከላከያ ሠራዊት #በኦሮሚያ ክልል እያደረገ ባለዉ የአሸባሪዉ ሸኔ ታጣቂዎች እርምጃ እየተወሰደባቸዉ ይገኛል።
መከላከያ #በወለጋ፣ እና #ጉጂ አከባቢዎች ልዩ ኦፕሬሽን እያደረገ ሲገኝ በዚህ እጅግ በጣም ብዙ የአሸባሪዉ ታጣቂዎች እየተደመሰሱ እና እየተማረኩ እንደሚገኝ ታዉቋል።
ይህ ልዩ #ኦፕሬሽን በክልሉ ሌሎች አከባቢዎችም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እና ሸኔን ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለማጥፋት ይሰራል ተብሏል።
12/12/2023
በአሸባሪው ሸኔ ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ እንደቀጠለ ነው ‼️
በምሰራቅ ሽዋና የምሰራቅ አርሲ ዞኖች የህብረተሰቡን ሰላም ለማስፈንና የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ በአሸባሪው የሸኜ ቡድን ላይ በሀገር መከላከያ ሰራዊት እየወሰዱ ያለው ርምጃ ውጤታማ መሆኑ እንደቀጠለ ነው!
የህዝብ ጠንቅ የሆነውን የሸኔ ቡድን ለማጥፋት በሚደረጉ ስምሪቶች ሁሉ የአካባቢው ማህበረሰብና በየደረጃው ያለ የፀጥታ አካላት በጋራ ቅንጅት በመሰራቱ በርካታ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ እየደረሰበት ነው!
የተማረኩ መሳሪያዎችንና ትጥቆችን በነበረው ስምሪት ሸኔ እንዲደመሰስ አብረው ከሰራዊቱ ጎን ተሰልፈው ለነበሩ የወረዳ አመራሮች ሰራዊቱ አስረክቧል።
12/12/2023
የሸኔ ጣረ_ሞት
ለህዝብ ጥቅም እሰራለሁ ከሚለው በተቃራኒ የቆመና የህዝቦችን #ስቃይ የሚያረዝም #ሽብርተኛ ሃይል ላይ እየተወሰደ ያለው #እርምጃ ከፍተኛ ኪሳራ እያደረሰበት መሆኑ ተነገረ።
በቡድኑ ላይ እየተወሰደ ባለው እርምጃ ከፍተኛ ኪሳራ እየደረሰበት እና እጅግ ከፍተኛ ቁጥር ያለው የፅንፈኛው ታጣቂዎችም እጃቸውን በሰላም እየሰጡ ስለመሆኑ መረጃዎች ያመለክታሉ።
በመከላከያ ሰራዊት የተማረኩ የሽብርተኛው ቡድን አባላትም:- ቡድኑ የምንታገለው ለኦሮሞ ህዝቦች ነፃነት ነው በሚል ወጣቱን ሃይል #በማደናገር ብዙዎችን ያሳሳተ የእኩይ አላማ ስብስብ መሆኑን ስለመረዳታቸው ገልጿል።
አሁን መንግስትና የፀጥታ ተቋማት እየወሰዱት ያለው የተጠናከረ #ዘመቻ ከሸኔ ጋር ተዳምሮ ቡድኑ የለየለት #አቅም ማነስ ውስጥ እንደሚገኝ ነው ምርኮኞቹ የሚናገሩት።
አመራሮችም በአሸባሪ ቡድኑ ውስጥ ያሉ ወጣቶችም እጃቸውን ለፀጥታ ተቋማት በመስጠት ራሳቸውን እንዲያድኑ ጥሪ አቅርበዋል።
12/12/2023
የመከላከያ ምት እና የሸኔ መፈረካከስ
ከሰሞኑ #መከላከያ እየወሰደ ባለው እርምጃ ቡድን እግር በእግር እየተከታተለ ዋጋውን እየሰጠው ይግኛን!
ህገ መንግስታዊ ስረአቱን ለማስጠበቅ እና ህገ መንግስታዊ ሃላፊነቱን ለመወጣት በቁርጠኝነት እየሰራ ያለው መከላከያ ሰራዊታችን የአሸባሪውን ሸኔ ብድን መዋቅር እየበታተነው ይገኛል።
ህዝብን #የሚዘርፍ ህዝቡን #የሚያሰቃይ ከጠላት ጋር የሚሰራው ይሔ የእናት ጡት ነካሽ የሆነውን ሽብርተኛ ቡድን እግር በእገ እየተከታተለ በመደምሰስ ላይ የሚገኛው መከላከያ ሰራዊት በሺዎች የሚቆጠሩ የሸኔ አባላትን መማረኩም ይታወቃል።
በተለይም #የኦሮሞ ህዝብ ይሔን የኦሮሞን ማንነት ለማጠልሸት የተፈጠረ አሸባሪ ቡድን ለማጥፋት ቆርጦ በመነሳት ከመከላከያ ጎን በመቆም ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል።
12/12/2023
በሸኔ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ቀጥሏል
በኦሮሚያ #ሆሮ ጉድሩ ወለጋ፣ #ቄለም ወለጋ፣ #ሰሜን ሸዋ አቦቴ እና #ጉጂ በጽንፈኛው ሸኔ ላይ ልዩ ኦፕሬሽን እየተደረገ ይገኛል።
በዚህም በጽንፈኛው #ሸኔ እየተወሰደ ያለው እርምጃ በከፍተኛ ሁኔታ እየተጧጧፈ ይገኛል።
ይህ ኦፕሬሽን #መከላከያ ሠራዊት፣ #ሪፐብሊካን ጋርድ እና #ኦሮሚያ ፖሊስ በጥምረት የተካሄደ ሲሆን፤ ከአርብ ጥዋት ጀምሮ እስካሁን ከሁለት ክፍለ ጦር በላይ በላይ የጽንፈኛው ታጣቂዎች ሲደመስሱ ከ 2300 በላይ የቆስሉ እና እጃቸዉን በሰላም የሰጡ የአሸባሪዉ አባላት በጸጥታ ሃይሉ ቁጥጥር ስር እንዳሉ ተገልጿል።
12/12/2023
በሸኔ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ቀጥሏል
ከመንግስት ለሰላም የተዘረጋለትን አልቀበል ያለው አሸባሪው ሸኔ አይቀጡ ቅጣት እየተቀጣ ይገኛል ። በኦሮሚያ ክልል በአንዳንድ ቦታዎች ሽብር እየፈጠረ የቆየው ሸኔ በከባድ ኦፕሬሽን ሙትና ቅስለኛ ከፊሉ ደግሞ እጅ በመስጠት የተለያዩ ቦታዎች ከአሸባሪው ቡድኑ እየጸዱ ነው ።
በቄለም ወለጋ ዞን በሳዲ ጨንቃ እና ዳሌ ዋበራ ወረዳዎች መከላከያ ከህዝብ ጋር በመሆን በአሸባሪው ሸኔ ላይ በወሰደው እርምጃ ከ 30 በላይ የሚሆኑ ሲደመሰሱ ሌሎች በሰላም እጃቸውን ለመከላከያ ሰጥቷል ። ይህ እንደ መዥገር በህዝባችን ላይ በመጣበቅ ያስቸገረው ፅንፈኛ ዋጋውን እያገኛ ነው ።
12/12/2023
ጀግነው መከላከያ ሰራዊት በአሸባሪው ሰኔ ላይ የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ ነው ‼️
በምዕራብ ሸዋ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች እየተዘዋወሩ የሰራዊቱን የተልዕኮ አፈፃፀም የተመለከቱት የኮሩ ሎጀስቲክስ ሃላፊ ኮሎኔል ኢያሱ ሃፍቱ ሠራዊቱ ግዳጅ የመፈፅም አቅሙን በማሳደግ በዞኑ እየተንቀሳቀሰ ማህበረሰቡን በማፈናቀል ለሰቃይና እንግልት ሲዳርግ የቆየውን ሸኔን መምታት መቻሉን ገልፀዋል።
ሰራዊቱ የተቋሙን ቁልፍ እሴቶች ተላብሶ ጠላትን እየደመሰሰ ህዝብና መንግስት የሠጡትን አደራ እየተዋጣ እንደሚገኝ የገለፁት ኮሎኔል ኢያሱ ህብረተሰቡ ሠላም ለማምጣት በሚደረገው እንቅስቃሴ አሥፈላጊ መረጃዎችን በመሥጠት እና ድጋፍ በማድረግ የበኩሉን አሥተዋፅኦ እየተወጣ መሆኑንም ተናግረዋል።
በተመሳሳይ ክፍለ ጦሩ በተሰማራበት የግዳጅ ቀጠና አሸባሪውን የሸኔ ቡድን እየደመሰሰ መሆኑን አሥታውቋል።
በምስራቅ ሸዋ ዞን በቦሰት ወረዳ በተለያዩ ቀበሌዎች አሸባሪው የሸኔ ቡድን በአከባቢው ማህበረሰብ ላይ ግፍና በደል ሲፈፅም የነበረ ቢሆንም አሁን ግን በተደረገው ዘመቻ በሽብር ቡድኑ ላይ የማያዳግም ርምጃ የተወሠደበት መሆኑን ሻምበል አንዷለም ሞገስ ተናግረዋል።
የሽብር ቡድኑ ይጠቀምባቸው የነበሩ ስናይፐር ፣ ክላሽ ፣ ትጥቅ ፣ ቦንብ እና የተለያዩ ዓይነት ጥይቶች መማረክ መቻሉንም ተነግሯል።
12/12/2023
መንግስት ተደጋጋሚ #ለሠላም እጁን ቢዘረጋም አሻፈረኝ ብሎ በህዝብ ላይ ጉዳት ሲያደርስ የቆየው የሽብር ቡድን በቁጥጥር እየዋለ እና የማያዳግም እርምጃ እየተወሰደበት ነው።
ከመከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ እንደሚያስረዳው ቡድኑ ላይ እየተወሰደ ባለው እርምጃ ከፍተኛ ኪሣራ እያስተናገደ ስለመሆኑ ተነገሯል።
አብዛኛው የቡድኑ ታጣቂ በሰላም እጁን ለሰራዊቱ እየሰጠ ሲሆን አሻፈረኝ ባሉት የታጣቂው አባላት ላይ በተወሰደ እርምጃም ብዙዎች #ሙት እና #ቁስለኛ ሆነዋል።
12/12/2023
ጥያቄ ለአቶ ታዬ...መንግስት እንደ እርሶ የታገሰዉ ማንን ነዉ?
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
Addis Ababa