Love_neba
SameloveoneSamelove2loveistrue
23/10/2025
የመንግስት ሠራተኞች ተሻሽሎ የወጣው አዋጅ 1353/2017 ስለ ዲሲፒሊን ቅጣት ምን ይላል? For your understanding.
ከባድ የዲሲፕሊን ቅጣት የሚያስከትሉ ጥፋቶች: ክፍል አስራ ሦስት አንቀፅ 98 #አዋጁ እንዲህ ይላል። www.csc.gov.et
+++++++++++++++++++++++++
1.ሕጋዊ_ትእዛዝን ባለማክበር፣ በቸልተኝነት፣ በማልገም፣ ወይም ሆነ ብሎ የአሠራር ሥነ-ሥርዓት ወይም የመንግስትን ፖሊሲ ባለመከተል በሥራ ላይ በደል ማድረስ፤
2. ጉዳዮችን ሆን ብሎ ማዘግየት ወይም ባለጉዳዮችን ማጉላላት፤
3.ተቋምን አደጋ ላይ በሚጥል ተግባር መሠማራት ወይም ሥራ እንዳይሰራ ሆን ብሎ ማወክ ወይም ከሚያውኩት ጋር መተባበር
4. በቀላል የዲስፕሊን ቅጣት እርምጃዎች ባለመታረም ያለበቂ ምክንያት ሦስት ቀንና ከዛ በላይ ሥራ ከቀረ ወይም የሥራ ሰዓት አለማክበር፤
5. በሥራ ቦታ በጠብ አጫሪነትን መደባደብ፤
6. በልማዳዊ ስካር ወይም በአደንዛዥ ዕፅ ሱስ በመመረዝ ሥራን መበደል፤
7. ጉቦ መቀበል ወይም እንዲሰጠው መጠየቅ፤
8. በሥራ ቦታ ለሕዝብ ሞራል ተቃራኒ የሆነ ድርጊት መፈጸም፤
9. የሌብነት ወይም የእምነት ማጉደል ድርጊት መፈጸም፤
10.የማታለል ወይም የማጭበርበር ድርጊት መፈጸም፤
11. በመሥሪያ ቤቱ ንብረት ላይ ሆን ብሎ ወይም በቸልተኝነት ጉዳት ማድረስ፤
12. በሥልጣን አለአግባብ መጠቀም፤
13. በሥራ ቦታ ላይ ፆታዊ ትንኮሳ ወይም ጥቃት መፈፀም እና
14.በዚህ አንቀፅ ከተዘረዘሩት ጋር ተመሳሳይ ክብደት ያለው ሌላ የዲሲፕሊን ጉድለት መፈፀም ።
_______________________________
ሠራተኛን ከሥራ አግዶ ስለማቆየት #አዋጁ ምን ይላል:
አንቀፅ 101 እና 2
++++++++++++++++++++++++++
1.ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ ከሥራ አግዶ ማቆየት የሚቻለው
(ሀ).ከተጠረጠረበት ጉዳይ ጋር አግባብነት ያላቸውን ማስረጃዎች በማበላሸት:በመደበቅ ወይም በማጥፋት ምርመራውን ያሰናክላል : ተብሎ ከታሰበ
(ለ).በመንግስት ንብረት ላይ ተጨማሪ ጉዳት ያደርሳል:ተብሎ ከታሰበ
(ሐ).ከተከሰሰበት ጥፋት ክብደት አንፃር የሌሎችን ሰራተኞች ሞራል የሚነካ ወይም የተገልጋዩን ሕዝብ በመሥሪያ ቤቱ ላይ ሊኖረው የሚገባውን እምነት ያዛባል:ተብሎ ከታሰበ
(መ).ተፈፀመ የሚባለው ጥፋት ከሥራ ያስወጣል ተብሎ ሲገመት
(ሠ).በአገልግሎት አሰጣጥ ተገልጋዩን ማጉላላቱ እና ማማረሩ ከበቂ መረጃና ማስረጃ ጋር ተያይዞ ለመንግስት መሥሪያ ቤቱ ሲቀርብ እና የመሥሪያ ቤቱን ገፅታ ያበላሻል :ተብሎ ሲገመት ነው።
2.በዚህ አንቀፅ ንዑስ አንቀፅ (1) መሰረት አንድ ሠራተኛ ከሥራና ከደሞዝ ታግዶ ሊቆይ የሚችለው ከሁለት ወር ለማይበልጥ ጊዜ ይሆናል።
11/08/2025
28/04/2025
22/04/2025
!!
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
Bole
Addis Ababa
0000
12/09/2025