Heni henok
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Heni henok, Health/Beauty, Addis Ababa.
16/05/2026
23/04/2026
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (Artificial Intelligence) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) ሆነው ተሾሙ። ሹመቱ የተሰጠው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በዘርፉ ላሳዩት አመራር እና ኢትዮጵያ በአህጉሩ የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የፈጠራ ሥራዎችን ለማስፋፋት እየተገበረች የምትገኘውን የላቀ ሚና እውቅና ለመስጠት ነው።
በተላከው የሹመት ደብዳቤ ላይ የሚከተለው ሰፍሯል፦ “የተከበሩ የእርስዎ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እና አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን ለማስፋፋት ያደረጉት አመራር፣ ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ለአፍሪካ ሉዓላዊነት፣ ለውጤታማነት እና ለአሳታፊ እድገት ቁልፍ መሣሪያ ሆኖ እንዲያገለግል በማስቻል ረገድ ትልቅ እገዛ አድርጓል። ስልታዊ በሆነ መልኩ የቴክኖሎጂ ነጻነትን እና ዐቅምን ለመገንባት የሚያደርጉት ተከታታይ ቅስቀሳ፣ አህጉሩ በኃላፊነት እና በፍትሐዊነት በታጀበ የሰው ሰራሽ አስተውሎት አጠቃቀም ረገድ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም እንዲሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ ይኖረዋል።”
ባለፉት ጥቂት ዓመታት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አመራር፣ ኢትዮጵያ በዲጂታላይዜሽን እና በሰው ሰራሽ አስተውሎት ዘርፎች ያስመዘገበችው እድገት ከፍተኛ አፈጻጸም ያሳየ ነው። የዲጂታል መሰረተ ልማትን ማስፋፋት፣ የኢ-መንግሥት (e-government) አገልግሎቶችን ሥራ ላይ ማዋል፣ በፈጠራ ሥነ-ምህዳር ላይ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ፣ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ኢንስቲትዩትን ማቋቋም እንዲሁም ሀገራዊ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስትራቴጂ መንደፍ ለለውጡ ጠንካራ መሰረት የጣሉ ተግባራት ናቸው። በተጨማሪም ራሱን የቻለ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ዩኒቨርሲቲ ለማቋቋም የታቀደው ዕቅድ፤ ምርምርን፣ የክህሎት ልማትን እና አህጉራዊ ትብብርን ይበልጥ እንደሚያጠናክር ይጠበቃል።
Prime Minister Abiy Ahmed has been appointed as the African Union Champion for Artificial Intelligence and Digital Health. The announcement recognises his leadership and Ethiopia’s growing role in advancing artificial intelligence and innovation across the continent.
The appointment letter noted: “Your Excellency’s leadership in promoting digital transformation and emerging technologies has helped position artificial intelligence as a key tool for sovereignty, efficiency, and inclusive growth in Africa. Your continued advocacy for strategic autonomy and technological empowerment will be instrumental in positioning the continent as a global leader in responsible and equitable AI adoption.”
Ethiopia’s progress in digitization and artificial intelligence launched and accelerated significantly under the Prime Minister’s active engagement over the last few years. Initiatives such as the expansion of digital infrastructure, the rollout of e-government services, investments in innovation ecosystems, and the establishment of an AI institute and development of a national AI strategy have laid a strong foundation for transformation. In addition, plans to establish a dedicated AI university are expected to strengthen research, talent development, and continental collaboration in emerging technologies.
23/04/2026
ዛሬ ጠዋት የአፍሪካ በሽታ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ከሆኑት ከዶክተር ዣን ካሴያ ጋር ውጤታማ ውይይት አድርገናል። በውይይታችን በተለያዩ ቅድሚያ የሚሰጣቸው ጉዳዮች ላይ የመከርን ሲሆን፤ በተለይም በአፍሪካ ሕብረት የሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) እና የዲጂታል ጤና ዘርፍ መሪ (Champion) በመሆን የተሰጠኝን አዲስ ኃላፊነት በሚመለከት በስፋት ተነጋግረናል።
የፈጠራ ሥራዎች ለአፍሪካ ዕድገት ምንጊዜም ወሳኝ መሰረት ናቸው። በጤናው ዘርፍ የሚገጥመንን ተለዋዋጭ ተግዳሮቶች ለመወጣት የሰው ሰራሽ አስተውሎትንና የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ዐቅም መጠቀም የጤና ሥርዓታችንን ለማጠናከር፣ ተደራሽነትን ለማስፋፋት እና ለሕዝባችን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ወሳኝ ነው። ኢትዮጵያ ያላትን ልምድ ለአህጉሩ ለማካፈል እንዲሁም በፍጥነት ከሚለዋወጠው የቴክኖሎጂው ዓለም ጋር ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመራመድ የሚያስችሉ ጠንካራ አጋርነቶችን ለመመሥረት ያላትን ቁርጠኝነት ዳግም ታረጋግጣለች።
ይህንን ርዕይ ወደ ተጨባጭና አካታች ውጤት ለመለወጥ ከአፍሪካ ሲዲሲ (Africa CDC) እና በመላው አህጉሪቱ ከሚገኙ አጋሮች ጋር በቅርበት ለመሥራት ዝግጁ ነኝ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አሕመድ(ዶ/ር)
17/04/2026
የመራጮች ምዝገባ 5 ቀን ብቻ ቀረው!!
እኔ በጊዜ የምርጫ ካርዴን ወስጃለሁ፤ እናንተስ?
እንደ ሰለጠኑት ሀገራት በእኛም ሀገር የመንግሥት ሥልጣን ከሕዝብ የሚመነጭና በሕዝብ የምርጫ ካርድ የሚወሰን መሆን አለበት፤ ይኖርበታልም።
ምርጫ በሁሉም አካባቢ ሰላማዊና የተረጋጋ ሁኔታ እንዲሰፍን፣ የዴሞክራሲ እና የሰለጠነ የፓለቲካ ሥርዓትን ለመገንባት፣ የተጀመሩ ልማቶችን ለማስቀጠል፣ እንዲሁም ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው።
ከምርጫ ውጪ የሚደረግ ማንኛውም እንቅስቃሴ በአገር ላይ ከፍተኛ ጥፋት ያመጣል።
ስለሆነም፤ ሁላችሁም የምርጫ ካርዳችሁን ወስዳችሁ የመምረጥ መብታችሁን ተጠቀሙ። መብታችሁን ተጠቅማችሁ ባትመርጡ፣ ሌሎች ተመዝግበው በመረጡት መንግሥት መተዳደራችሁ የማይቀር መሆኑን በመገንዘብ መብታችሁን ተጠቀሙ።
የምርጫ ካርድ ወስዶ መምረጥ ለሀብታሙም፣ ለደሃውም፣ ለተማረውም፣ ላልተማረውም፣ ዕድሜው ለመምረጥ ለደረሰ ወጣት፣ ለጎልማሳው፣ ለአዛውንቱ፣ ለሴቱም ሆነ ለወንዱ፣ ለባለስልጣንም፣ ለሌላውም ዜጋ እኩል የተሰጠ መብት ስለሆነ መብታችሁን ተጠቀሙበት!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Website
Address
Addis Ababa