Sidama Public Health Institute Communication Affairs
Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Sidama Public Health Institute Communication Affairs, Health/Beauty, Awassa.
03/06/2026
የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በዲጂታል ጤና ላይ የሚሠራውን የጥናት ፕሮፖዛል ሴሚናር አካሄደ።
የሲዳማ ክልል የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ግንቦት 26/2018 ዓ.ም
የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዘወትር በየሁለት ሳምንት በሚያካሄደው መደበኛ የምርምር ሴሚናር ላይ "በሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በመንግሥት ሆስፒታሎች የዲጂታል ጤና አተገባበር ዝግጁነት " በሚል ርዕስ የተዘጋጀ የምርምር ፕሮፖዛል በኢንስቲትዩቱ ከፍተኛ ተመራማሪ በዶ/ር አመሎ ቦልካ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሂዷል።
የጥናቱ ዋና ዓላማው በክልሉ ውስጥ የሚገኙ የመንግሥት ሆስፒታሎች ወደ ዲጂታል የጤና አሰራር ለመሸጋገር ያላቸውን ዝግጁነት፣ አቅምና ውስንነት በሳይንሳዊ መንገድ በመፈተሽ የጤና አገልግሎት አሠጣጥን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ እድገቶች ጋር ለማጣጣም ያለመ ነው።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ በበኩላቸው ፤ ጥናቱ በጤናው ዘርፍ ለሚቀረጹ ፖሊሲዎችና የአሠራር ሥርዓቶች ሳይንሳዊ መረጃዎችን በማመንጨት ለውሳኔ ሰጪዎች ጠቃሚ ግብዓት እንደሚሆን ገልጸዋል።
በሴሚናሩ ላይ በጥናቱ ስልት (Methodology)፣ የመረጃ አሰባሰብ ሂደት እና ጥናቱ ሊያስገኝ በሚችለው ጠቀሜታ ዙሪያም ሰፊ ውይይት ተካሂዶ፤ ከተሳታፊዎች የቀረቡ አስተያየቶች ጥናቱን የበለጠ የሚያጠናከሩ በመሆናቸው በፕሮፖዛሉ ውስጥ እንዲካተቱ ተደርጓል።
የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ግንቦት 26/2018 ዓ/ም
ሀዋሳ
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ
ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794
Web site: sphi.gov.et/emergency
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=100083576610173
Telegram: https://t.me/c/1865772308/1
Email:- [email protected]
01/06/2026
የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ዋና ዳይረክተር ዶ/ር ዳመነ ዳባልቄ በሲዳማ ክልል በደቡባዊ ዞን በሁላ 01 ምርጫ ጣቢያ በመገኘት ድምፃቸዉን ሰጥቷል ::
#ኢትዮጵያእየመረጠችነው !
የሲዳማ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ግንቦት 24/2018 ዓ/ም
ሀዋሳ
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች
👇👇👇👇 ይመልከቱ
ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794
Web site: sphi.gov.et/emergency
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=100083576610173
Telegram: https://t.me/c/1865772308/1
Email:- [email protected]
27/05/2026
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1447ኛ የኢድ አል-ዓደሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤
ኢድ ሙባረክ!
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ፣ የመረዳዳት እና የአብሮነት እንዲሆንላችሁ የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ይመኛል።
የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ግንቦት 19/2018 ዓ/ም
ሀዋሳ
ለተጨማሪ መረጃዎች:
ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794
Web site: sphi.gov.et/emergency
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=100083576610173
Telegram: https://t.me/c/1865772308/1
Email:- [email protected]
26/05/2026
ኢትዮጵያን ወደ ተምሳሌት ሀገር” በሚል መሪ ቃል ለ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ በክልል ደረጃ የብልፅግና ፓርቲ የ“ምረጡኝ” ቅስቀሳ በሀዋሳ ከተማ የአለማቀፍ እስታዲየም የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት አመራሮችና አባላት በነቂስ ወጥተው ድጋፋቸውን አሳይቷል ።
የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ግንቦት 18/2018 ዓ/ም
ሀዋሳ
ለተጨማሪ መረጃዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት:
ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794
Web site: sphi.gov.et/emergency
Facebook: https://web.facebook.com/profile.php?id=100083576610173
Telegram: https://t.me/c/1865772308/1
Email:- [email protected]
25/05/2026
በአፍሪካ ስለተከሰተው ኢቦላ ቫይረስ በሽታ እና በኢትዮጵያ እየተደረጉ ያሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች
ግንቦት 17 ፣ 2018 ዓ.ም
የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) በግንቦት 09 ፣ 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኦፍ ኮንጎ (DRC) እና በዩጋንዳ በቡንዲቡግዮ (Bundibugio) ቫይረስ ዝርያ የሚመጣ የኢቦላ ቫይረስ በሽታ መከሰቱን ያሳወቀ ሲሆን እስከ ትላንት ግንቦት 16፣ 2018 ድረስ በእነዚሁ ሀገራት በአጠቃላይ ከ101 በላይ የሚሆኑ በላቦራቶሪ የተረጋገጡ ታማሚዎች እና ከ900 በላይ ንክኪ ያላቸው ተጠርጣሪዎች የህክምና ክትትል ላይ ይገኛሉ።
የኢቦላ ቫይረስ በሽታ ከፍተኛ የስርጭት እና የሞት ምጣኔ ያለው በሽታ ሲሆን ከሰው ወደ ሰው በንክኪ በቀላሉ ይተላለፋል።
እስከዛሬ ድረስ በሃገራችን ኢትዮጵያ ምንም አይነት በኢቦላ ቫይረስ በሽታ የተጠረጠረ ወይም የታመመ ሰው አልተገኘም።
ምንም እንኳን በሽታው ከተገኘባቸው አገራት ጋር ቀጥተኛ የድንበር ግንኙነት ባይኖረንም የበሽታውን አደገኛነት በመገንዘብ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) እና የአፍሪካ በሽታ ቁጥጥርና መከላከል ማዕከል (Africa CDC) የወረርሽኙን መከሰት ይፋ ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና ጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ፦
- በሁሉም አለም አቀፍ የየብስ መግቢያ እና መውጫ ኬላዎች የልየታ እና የቅኝት ስራዎች በማጠናከር ፣
- በአለም አቀፍ አየር ማረፊያዎች የተጠናከረ ክትትል በማድረግ ፣
- የጤና ተቋማት ዝግጁ በማድረግ እንዲሁም የላቦራቶሪ አቅምን በማሳደግ
- እንዲሁም አስፈላጊው የህክምና ግብአት አቅርቦት ላይ የተጠናከረ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እየተከናወነ ይገኛል።
Website: ephi.gov.et
25/05/2026
ኢንስቲትዩቱ በላብራቶሪ አቅም ግንባታ እና ጥራት ማስጠበቅ
በጤናው ዘርፍ የላብራቶሪ አቅም ግንባታ እና ጥራት ማስጠበቅ (Laboratory Capacity Building and Quality Assurance) የሕክምና አገልግሎት ጥራት፣ የታካሚዎች ደህንነት እና የሕዝብ ጤና ጥበቃ ዋና መሠረት ነው። የላብራቶሪ ምርመራ ውጤት ሐኪሞች ለሚሰጡት ውሳኔ ከ70 በመቶ በላይ ድርሻ እንዳለውም ይገመታል። ለዛም ነው ላብራቶሪ የህክምናው ዘርፍ የጀርባ አጥንት ነው የሚባለው፡፡ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩትም የላብራቶሪ አቅምን ለመገንባትና ጥራትንም ለማረጋገጥ በርካታ ስራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡
በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በላብራቶሪ አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የላብራቶ ጥናት ትግበራ ዲቪዢን ሃላፊ አቶ አዋድ መሃመድ እንደሚናገሩት የኢትዮጵያ የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የሪፈራል እና ሪፈረንስ ላብራቶሪ ዳይሬክቶሬት በየጊዜው አዳዲስ ምርመራዎችን እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡ በዚህ አመትም በጣም ብዙ የላብራቶሪ ምርመራዎችን ማስተዋወቅ ተችሏል። ብዙ ገንዘብና ግዜ የሚወስዱ በውጪ ሀገር የሚሰሩ የላብራቶሪ ምርመራዎችን በዝቅተኛ ዋጋ ለህብረተሰቡ ማቅረብ ችሏል፡፡ ለህብረተሰብ ጤና አስተዳደር የሚያስፈልጉ ምርመራዎችንም በየጊዜው እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡
እነዚህ የሪፈራል እና ሪፈረንስ ላብራቶሪዎች ከጥራት አኳያ ሲታዩ በISO 15189 የጥራት እውቅና የተሰጣቸው ናቸው፡፡ ISO 15189 ደግሞ ለሜዲካል ላብራቶሪ የተዘጋጀ አለም አቀፍ የጥራት ደረጃ ነው። በኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ያሉት የሪፈራል ላብራቶሪዎች ሁሉም ይህንን የጥራት መስፈርት አሟልተዋል፡፡ ይህም ላብራቶሪዎቹ በየትኛውም አለም ተቀባይነት እንዲኖራቸው ያደርጋል፡፡
አሁን ላይ ደግሞ አንቲ-ዶፒንግ (Anti-Doping) ምርመራ በሀገር አቀፍ ደረጃ ማድረግ የሚያስችል አቅም ተፈጥሯል:: ይህም በቅርቡ የሚጀመር ይሆናል፡፡ ብዙ ጊዜ አትሌቶች ይህን ምርመራ የሚያደርጉት በውጪ ሀገር ነበር፡፡ አሁን ላይ ግን ይህን ምርመራ በሀገር ውስጥ ማድረግ ተችሏል፡፡ ስለዚህ ወደፊት ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለጎረቤት ሀገራትም ጭምር ምርመራ ለማድረግ የሚያስችል አቅም ተገንብቷል፡፡
ሌላው የላብራቶሪ አቅም ግንባታ ስራ የሚሰራው አጠቃላይ የላብራቶሪ አገልግሎት ጥራታቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ ድጋፍ ማድረግ ሲሆን እንደ ኢትዮጵያ የላብራቶሪ አገልግሎት ጥራትን በሶስት መንገዶች እንዲጠበቅ ይደረጋል፡፡ አንደኛው ለጤና ተቋማት የተዘጋጁ የጥራት መጠበቂያ ስረአትን ተግባራዊ በማድረግ ነው፡፡ ሁለተኛ ደግሞ በዋነኝነት ለሆስፒታል ላብራቶሪ የተዘጋጀውን የጥራት ማስጠበቂያ ፕሮግራም ተግባራዊ እንዲደርጉ በማድረግ ሲሆን ሶተኛውና የመጨረሻው የክልል ሪፈራል ላብራቶሪዎች እና ሀገር አቀፍ ሪፈራል ላራቶሪዎች የአለም አቀፍ ስታንዳርድ ማለትም የ15185 (15189) ተግባራዊ እንዲያደርጉ የሚያወጡት የምርመራ ውጤት ታማኝነት እንዲኖረው የሚያረጋግጥ ስራ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በዋናነት ይሰራል፡፡
ስለዚህ አጠቃላይ የክልል፣ ሆስፒታል፣ የፌደራል ሆስፒታሎች ላብራቶሪዎች ላይ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩ የላብራቶሪ ጥራት ተግባራዊ እንዲሆን ድጋፍ ያደርጋል። በተዋረድ ደግሞ የክልል ሪፈራል ላብራቶሪዎች የራሳቸውን እና በስራቸው ያሉ ፋሲሊቲዎችንድጋፍ ያደርጋሉ፡፡ ስለዚህ ኢንስቲትዩቱ የክልል ሪፈራል ላብራቶሪዎችን ወይም የህዝብ ጤና ኢንስቲትዩቶችን ይደግፋል፡፡
ስለዚህ እነሱ ደግሞ በተዋረድ ወደ ታች ላለው ላብራቶሪ ተመሳሳይ ድጋፍ ያደርጋሉ፡፡ ኢንስቲትዩቱም አቅም በየቦታው እየገነባ ነው ያለው፡፡ የክልል ሪፈራል ላብራቶሪዎች ደግሞ በተዋረድ የድጋፍ ስራቸውን ይሰራሉ፡፡ ከዚህ አንፃር ጥራትን ለማስጠበቅ የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ይሰራል፡፡
ስለዚህ እንደ ሀገር በኢትዮጵያ የISO 15189 የጥራት ደረጃን ያሟሉ ወደ 75 የሚሆኑ ላብራቶሪዎች አለም አቀፍ እውቅና አግኝተዋል። ነገር ግን አሁን ካሉት 4,500 በላይ ላብራቶሪዎች ቁጥር አንፃር ሲታይ ገና ነው፡፡ ስለዚህ እዚህ ላይ ወደፊት ብዙ ስራ መሰራት እንዳለበት የሚጠቁም ነው። እንዲያም ሆኖ ኢትዮጵያ የላብራቶሪ ጥራት ቁጥጥር ስረአትን ተግባራዊ በማድረግ እና የISOን እውቅና በማምጣት በአፍሪካ አራተኛ ደረጃ ይዛለች፡፡
ይህም እንደ አፍሪካ ኢትዮጵያ በጣም ጥሩ ደረጃ ላይ እንደምተገኝ ያሳያል፡፡ ነገር ግን ደግሞ ባጠቃላይ ሲታይ የጥራት ቁጥጥር ስረአት ወይም ደግሞ የጥራት ደረጃ አሁንም ገና የሚቀረው መሆኑን ያሳያል፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ ደረጃ በአፍሪካ ጥሩ ቢሆንም እንደ ሀገር ካሉት የላብራቶሪዎች ብዛት አንጻር አሁንም በጣም ብዙ መስራት ይጠበቃል፡፡
አቶ አዋድ እንደሚሉት ሌላው ከላብራቶሪ ጥራት ጋር ተያይዞ ያለው ፕሮግራም የውጪ ጥራት ምዘና (External Quality Assessment) ሲሆን ይህም ላብራቶሪዎች የሚሰሯቸው ስራዎች ታአማኒነታቸውን የሚከታተል ስረአት ነው፡፡ በዚህም ውስጥ ሶስት አይነት ስረአቶች አሉ፡፡ አንደኛው እንዲሞከሩና በትክክል ይሰራሉ ወይስ አይሰሩም የሚለውን ለማየትና ጥራታቸውን ለማረጋገጥ እንደ ሀገር ከውጭ ኮንትራት ተደርጎ የሚመጣ የውጪ ጥራት ምዘና ነው፡፡
ሁለተኛው ደግሞ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰራ ፒቲ ፓናል አለ። ስለዚህ እነዚህን በመጠቀም የላብራቶሪ አቅማቸውን ከጥራት አንጻር መመዘኛ ስረአት ሲሆን ላብራቶሪዎቹ በትክክል አገልግሎት እየሰጡ መሆኑንና አለመሆኑን ያረጋግጣል፡፡ ከዚህ ውስጥ አንደኛው ድጋሚ ማረጋገጥ ወይም (Re-checking) ስረአት ሲሆን ይህም ላብራቶሪዎች የሰሩትን ናሙና ወይም ስላይድ በትክክል ነበረ ወይ የሰሩት የሚለውን ነገር በድጋሚ የማረጋገጥ ስራ የሚሰራበት ነው፡፡ ።
ሶስተኛው ደግሞ ኦንሳይት ኢቫሉዌሽን (On-site evaluation) ነው። ላብራቶዎች እየሰጡት ያለው አገልግሎት ከጥራት አንፃር ልክ ነበረ ወይ የሚለውን አጠቃላይ ስረአቱን ክትትል የሚደረግበት ነው፡፡ ስለዚህ እነዚህን ሶስት መንገዶች በመከተል ላብራቶሪዎች የሚሰጡት አገልግሎት ጥራቱን የጠበቀ የተጠበቀ መሆኑን፣ እምነት የሚጣልበት መሆኑን እና በትክክለኛው ጊዜ መውጣት መቻሉን ለማረጋገጥ የኢትጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከክልል ሪፈራል ላብራቶሪዎች ጋር በመሆን ድጋፍ ያደርጋል፡፡ ኢንስቲትዩቱ በተዋረድ በአብዛኛው የክልል ሪፈራል ላብራቶሪችንና የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩቶችን አቅም ከማሳደግ አንጻር አጠቃላይ ድጋፍ ያደርጋል፡፡
ከዚህ ጋር ተያይዞ አንደኛው በኢንስቲትዩቱ እየተሰራ ያለ ስራ አለ። በናሽናል ደረጃ የኢኪውኤ (EQA) ሳምፕል ለማምረት የሚያስችል እቅድ ተይዟል፡፡ የህንፃ ግንባታው ተከናውኗል፡፡ ይህም ወደፊት በሀገር አቀፍ ደረጃ ብዙ ተሳታፊዎችን በዚህ ስረአት ውስጥ ማስገባት ያስችላል፡፡ በተጨማሪ ደግሞ ከዋጋ አንጻርም ሲታይ በጣም ብዙ የሚታደግ ስራ ነው።
23/05/2026
የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኩፍኝ ላቦራቶሪ ምርመራ በይፋ ተጀመረ።
የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ግንቦት 15/ 2018ዓ.ም
በሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የኩፍኝ ላቦራቶሪ ምርመራ በይፋ መጀመሩ ተገልጿል ።
ይህም በክልሉ እና በአጎራባች ክልሎች ለሚከሰቱ ወረርሽኞች ፈጣንና ተደራሽ የሆነ የላቦራቶሪ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ጉልህ እመርታ መሆኑ ተጠቁሟል።
ኢንስቲትዩቱ በተለያዩ የህብረተሰብ ጤና አደጋዎችና ወረርሽኞች ላይ ውጤታማ ምላሽ ለመስጠት የላቦራቶሪ አቅሙን በዘመናዊ መሳሪያዎችና በሰው ኃይል እያጠናከረ መሆኑ ተገልጿል።
ከኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በትብብር ለባለሙያዎች የተሰጠውን ስልጠና ተከትሎ የኩፍኝ ተጠርጣሪ ናሙናዎች በተቋሙ ውስጥ መመርመር መጀመሩ ተገልጿል።
በስልጠናው ላይ የተገኙት የሲዳማ ክልል ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የላቦራቶሪ ዳይሬክተር አቶ አዳቶ አዴላ እንደገለጹት፣ ከስልጠናው በኋላ የተሰበሰቡ ሁሉም የኩፍኝ ናሙናዎች በተቋሙ ውስጥ ተመርመረው ውጤታቸው መሰጠቱን ገልጸዋል።
አቶ አዳቶ አክለውም፣ ከዚህ ቀደም ወደ አዲስ አበባ በመላክ የሚከናወነው የኩፍኝ ምርመራ አሁን በኢንስቲትዩቱ ውስጥ ሙሉ በሙሉ መከናወን መጀመሩን ጠቅሰው፣ ይህም የምርመራ ጊዜን በማሳጠር ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ትልቅ አስተዋጽዖ እንደሚኖረው ተናግረዋል ።
በተጨማሪም የህብረተሰብ ጤና አደጋዎችን በፍጥነት የመለየት፣ የመከላከል እና ውጤታማ ምላሽ የመስጠት አቅምን ለማሳደግ የላቦራቶሪ አገልግሎቶች በአለም አቀፍ ጥራት ደረጃ መሰጠታቸው አስፈላጊ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተው አብራርተዋል ።
ጠንካራ የጤና ስርዓት ለመገንባት ዘመናዊና ተደራጅተው የሚሰሩ ላቦራቶሪዎች የጤና ዘርፉ “የጀርባ አጥንት” መሆናቸውም ተጠቅሷል።
የኩፍኝ ምርመራው በክልሉ ውስጥ መጀመሩ ታካሚዎች ፈጣን አገልግሎት እንዲያገኙ፣ የናሙና መጓጓዣ ወጪና ጊዜ እንዲቀንስ እንዲሁም ለወረርሽኝ ቁጥጥር ስራዎች የተሻለ የመረጃ ፍሰት እንዲኖር አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።
የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ግንቦት 15/2018 ዓ/ም
ሀዋሳ
ለተጨማሪ መረጃዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት:
ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794
Web site: sphi.gov.et/emergency
22/05/2026
20/05/2026
የሲዳማ ክልል የህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ለዞኖች፣ ለወረዳዎችና ለጤና ተቋማት የኮምፒውተር ድጋፍ አደረገ።
የሲዳማ ህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ግንቦት 12/2018 ዓ.ም
የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንሰቲትዩት ከ 12,283, 000 ብር በላይ ተገዝቶ የተበረከተለትን 111 ኮምፒዩተር ዴስክ ቶፕ በክልሉ ለሚገኙ ለሁሉም ዞኖች፣ ወረዳ ጤና ጽ/ቤቶች እና ሆስፒታሎች እንዲሁም ከፍተኛ ቁጥር ተገልጋዮችን ለሚያገለግሉ ጤና ጣቢያዎች የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቁጥጥር መረጃ አስተዳደርን ለማዘመን / PHEM &IDSR Digitalization/ ድጋፍ ማድረጉን አስታውቋል ።
በርክክቡ ወቅት መልዕክት ያስተላለፉት የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳመነ ደባልቄ በመልዕክታቸው ፦ድጋፉ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቁጥጥር መረጃዎችን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ዘላቂ እና ዘመናዊ የመረጃ አስተዳደር ሥርዓት ለመገንባት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ተናግረዋል ።
በመጨረሻም ዋና ዳይሬክተሩ የተረከቡትን ኮምፒውተሮች ለታለመላቸው ዓላማ እና የሥራ ክፍል ብቻ በአግባቡ እንዲጠቀሙ አሳስበው፣ ጤናማ ማኅበረሰብ ለመገንባት በመረጃ የተደገፈ የጤና ሥርዓት መገንባት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ትብብር እንደሚጠይቅ ጠቁመዋል።
ድጋፉን የተረከቡት የዞን ጤና ዴስኮች፣ የወረዳ ጤና ጽ/ቤቶች ፣ የሆስፒታል ኃላፊዎች፦ የሕብረተሰብ ጤና ድንገተኛ አደጋዎች ቁጥጥር መረጃዎችን በአንድ ሥርዓት ሥር በማደራጀትና በመተንተን የተሻለ የውሳኔ አሰጣጥ ሥርዓት ለመፍጠር እንደሚያስችል ተናግረው፥ የተደረገላቸውን ድጋፍ አድንቀው ለኢንስቲትዩቱ ምስጋና አቅርበዋል ።
የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ግንቦት 12 /2018 ዓ/ም
ሀዋሳ
ለተጨማሪ መረጃዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት:
ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794
Web site: sphi.gov.et/emergency
19/05/2026
የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በመድኃኒት የተላመዱ ተዋህስያን መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ የምክክር መድረክ ማካሄዱ ተገለጸ
የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ግንቦት 11/2018 ዓ.ም
የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በመድኃኒት የተላመዱ ተዋህስያን መከላከልና መቆጣጠር ዙሪያ የምክክር መድረክ ማካሄዱን አስታውቋል ።
በመድረኩ ላይ ጸረ ተዋህስያን መድሃኒቶችን በትክክል መጠቀም፣ መድሃኒቶችን የተላመዱ ተዋህስያንን በፍጥነት መለየት እና ተገቢ ህክምና መስጠት ላይ አጽንዖት ተሰጥቷል።
የሲዳማ ክልል ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት የላቦራቶሪ ዳይሬክተር አቶ አዳቶ አዴላ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት፣ በሆስፒታሎች የማይክሮባዮሎጂ ላቦራቶሪ አቅምን ማጠናከር እና ማስፋፋት ወቅታዊ አስፈላጊነት እንዳለው ገልጸው፣ በዚህ ረገድ የአቅም ግንባታ ስራዎች በእቅድ ተይዘው እየተከናወኑ መሆናቸውን አስታውቀዋል።
መድረኩ መድሃኒቶችን የተላመዱ ተዋህስያንን ለመቆጣጠር የተቀናጀ ስራ እና የተቋማት ትብብር ወሳኝ መሆኑን አመላክቷል ።
በውይይት ወቅት ተሳታፊዎች አንዳንዶች በሰጡት አስተያየት መድሃኒቶችን ያለ ሐኪም ምክር መጠቀም፣ አላስፈላጊ የፀረ-ተዋህስያን አጠቃቀም ችግሩን እያባባሰ መሆኑን ጠቅሰው፣ ህብረተሰቡን በማስተማር እና የጤና ተቋማት ቁጥጥርን በማጠናከር ችግሩን መቀነስ በትብብር መስራት እንዳለበት አሳስበዋል።
በውይይቱ የተሳተፉ ባለድርሻ አካላትም የኢንስቲትዩቱን ላቦራቶሪ በመጎብኘት የሚሰጡ አገልግሎቶችንና የተገነባውን የላቦራቶሪ አቅም ተመልክተዋል።
የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት
ግንቦት 11/2018 ዓ/ም
ሀዋሳ
ለተጨማሪ መረጃዎች የሲዳማ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት:
ነፃ የስልክ መስመር፡ 7794
Web site: sphi.gov.et/emergency
Click here to claim your Sponsored Listing.
Category
Contact the business
Website
Address
Awassa